አንድ ጠንካራ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ ማህበረሰብ አብረን እንገንባ!

ንቁ ተሳትፎ፣ ትርጉም ባለው ፖሊሲ እና በማህበረሰብ ተሳትፎ የህብረተሰባችንን የወደፊት ህይወት በመቅረጽ ይቀላቀሉን።

በለጠ ሞላ ጌታሁን(ዶክተር)

የዓብን ሊቀመንበር

"የተሻለች ኢትዮጵያን የሚፈልጉ ኃይሎች እንዲሰባሰቡ ጥረት እናደርጋለን። አገራችን እንድታድግ፣ የዜጎቿ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ ዲሞክራሲዊ ስርዓት እንዲጎለብት የማድረግ ኃላፊነትን ተቀብለን ተነስተናል።"

በለጠ ሞላ (PhD) - Party Chair
የዓብን ሊቀመንበር

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች እና ዝመናዎች

የዓብን አዲስ መግለጫ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ዓብን የሻቢያ መንግስት በኢትዮጵያ የዉስጥ ጉዳይ የሚያደርገዉ ጣልቃገብነት ቀጥሏል ሲል ገለጸ።

መጪ ኩነቶች

በማህበረሰብ ዝግጅቶች፣ ስብሰባዎች እና እንቅስቃሴዎች ውስጥ ይሳተፉ።

ኩነቶች የሉም

ራዕይ እና ተልዕኳችን

እያንዳንዱ ድምጽ የሚሰማበት፣ እያንዳንዱ ግለሰብ እኩል እድሎች የሚያገኝበት እና ህዝቦች ሁሉን ባሳተፈ አስተዳደር የሚያድጉበትን መንገድ ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል።

  • ራዕያችን፣ የፖለቲካ ተሳትፎ ከድምጽ መስጫ ባለፈ ቀጣይነት ያለው የዜጎች ተሳትፎ፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውይይት እና በሁሉም የአስተዳደር እርከኖች ላይ የትብብር ውሳኔዎችን ያካትታል።
  • ዴሞክራሲዊ የሆነ ግልጽ አሰራር ለሁሉም ተደራሽ የሚሆንበት፣ የተለያዩ አመለካከቶች ዋጋ የሚሰጡበት፤ ፖሊሲዎች የማህበረሰቡን እውነተኛ ፍላጎቶች እና ምኞቶች የሚያንፀባርቁበትን ምህዳር እንፈጥራለን።
  • አመራሩ ግልጽ እና ተጠያቂነት ያለው፣ ማስረጃ እና ስነምግባር የፖሊሲ ልማትን የሚመራበት እና የበለጠ ፍትሃዊ፣ ቀጣይነት ያለው እና የበለጸገ ማህበረሰብን ለአሁኑ እና ለመጪው ትውልድ ትኩረት የሚሰጥበት አሰራር እንዘረጋለን፡፡
  • ለአዎንታዊ ማህበራዊ ለውጥ እና እኩልነት ጥምረት መገንባት።
ተጨማሪ
Our Vision and Mission

እያደገ ያለው ማህበረሰባችንን ይቀላቀሉ።

ለአዎንታዊ ለውጥ የቆመ እንቅስቃሴ አካል ይሁኑ። ዛሬ ይቀላቀሉን እና ለሁሉም የተሻለ የወደፊት ሁኔታን ለመቅረጽ ያግዙ።

አባል ይሁኑ

ፓርቲያችንን ይቀላቀሉ እና ፖሊሲን እና ተነሳሽነትን ይቅረጹ።

አሁን ይቀላቀሉ

በጎ ፈቃደኝነት

ዘመቻዎቻችንን እና የማህበረሰብ ዝግጅቶችን ይደግፉ።

ተሳተፍ

በክስተቶች ላይ ተገኝ

በእኛ ዝግጅቶች እና የማህበረሰብ ስብሰባዎች ላይ ይሳተፉ።

የቀን መቁጠሪያ ይመልከቱ

ድጋፍ ያድርጉ

በገንዘብ ድጋፍ የፓርቲ ተልእኮ እንዲቀጥል ይርዱ።

አሁን ይለግሱ
ንቅናቄያችንን ተቀላቀሉ

ከአባላቶቻችን አንደበት!

የእኛን ማህበረሰብ የሚወክሉ የተለያዩ ድምፆች

በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን ) ከምስራታው ጀምሮ በተለያዩ ክፍሎች ተመድቤ ሳገለግል የነበረ እና አሁንም በማገልገል ላይ እንደሆኩኝ የሚታወቅ ነው። በዚህም መሰረት ፓርቲያችን አብን በቅደም ተከተል ባስቀመጣቸው ፍኖተ ካርታ በመመራት ህዝብ ከማንቃት ወደ ማደራጀት በመውሰድ የአማራ ህዝብ ጥያቄ በሁሉም ዘንድ እንዲታወቁና ምላሽ እንዲሰጣቸው ታግሎ በማታገልደረጃ ከፍተኛ ድርሻ አለው። በዚህም መሰረት አብን በሰላማዊ ትግልን ውጤት እንደሚገኝ አስተማሪ ድርጅት እንደሆነ የመጣንበት መነሰገድ ያሳያል። ስለሆነም መንግስት የአማራ ህዝብ ጥያቄ በመረዳት አለማቀፍ ተቋሟትም የአማራ ህዝብ ጥያቄን እንዲያውቁ እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጥያቄዎቻችንን ተረድተው የጋራ ሀገራችን ዲሞክራሲያዊ እና የመድበለ ፓርቲ ስርአት የተገነባባት እና አንድነቷ ተጠብቆ ለሁሉም ዜጎቿ ምቹ ሀገር ለመገንባት በትግል ላይ እንገኛለን ።

ኤረሚሰ ተገኝ

ኤርሚያስ ተገኝ

ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ አባል

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን) አባል ከሆንኩበት ጊዜ ጀምሮ ዓብን በሀገራችን የሚገባውን ትኩረት ያላገኙ የማህበረሰባችን ክፍል አካልጉዳተኞች ዋና የአካል ጉዳተኞች ህግ ሰራሽ ክፍተቶችን እንዲሴተካከሉ ለመታገል አካል ጉዳተኛን ወደፊት ማምጣት እና በአመራርነት በማካተቱ የህዝብ ድርጅት እንደሆነ የታየበት ሒደት ነው ። አካል ጉዳተኛው በተፈጥሮም ይሁን በሰውሰራሽ በሚታይበት ጉዳት ሲደርስባት የነበረውን የአመለካከት ፣ እነረዲሁም በህግ ማእቀፍ የሚታዩትን መገለል ለማስቆም እንዲሁም በሚፈጠሩ ችግሮች ዋና የግፍ ተቋዳሽ እና ግንባር ቀደም ተጠቂ እንደመሆናቸው በተጨማሪ በአማራነታቸው የሚደርስባቸውን በደል እና መገለል በራሳቸው ድምፅ እንዲያሰሙ እና ውክልናቸው እንዲረጋገጥ የአካታችነትን መርህ ፓርቲያችን አብን በመከተሉ ኩራት ይሰማኛል ። በተለያዩ መድረኮች የአማራ ህዝብ በደል እና በተለይ አካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እና ህግ ወለድ ችግሮች ድምፅ በመሆን እንዲሁም ጥያቄዎቻችን በፖሊሲ ማእቀፍ በሚጋባ የማታገያ አጀንዳ በመሆኑ ወደ ፓርቲው እንድቀላቀል አስገድዶኛል በቀጣይም አካል ጉዳተኞች በማደራጀት በፖለቲካ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ አበክረን እንሰራለን።

ሚካኤል ጫኔ

አብርሃም አባተ

የአካል ጉዳተኞች ክንፍ አባል

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን) አባል ከሆንኩበት ጊዜ ጀምሮ አብን ሴቶች 50+ የማህበረሰባችን ክፍል እንደመሆናቸው በአሳታፊነት በማካተቱ የህዝብ ድርጅት እንደሆነ የታየበት ነው ። የአማራ ሴት ሲደርስባት የነበረውን ለማስቆም እንዲሁም ዋና የግፍ ተቋዳሽ እና ግንባር ቀደም ተጠቂ እንደመሆኗ ሴቶች የራሳቸውን በደል በራሳቸው ድምፅ እንዲያሰሙ እና ውክልናቸው እንዲረጋገጥ የአካታችነትን መርህ ፓርቲያችን አብን በመከተሉ ኩራት ይሰማኛል ። በተለያዩ መድረኮች የአማራ ህዝብ በደል እና በተለይ ሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ድምፅ መሆን እንዲሁም በሚጋባ የማታገያ አጀንዳ በመሆኑ ትልቅ አክብሮት አለኝ በቀጣይም የሴቶች ተደራሽ ላይ አበክረን እንሰራለን።

Bety

ቤተልሄም አበራ

አባል

እንደተዘመኑ ይቆዩ

የቅርብ ጊዜ ዝመናዎችን፣ ዜናዎችን እና የክስተት ማስታወቂያዎችን ለመቀበል ለጋዜጣችን ይመዝገቡ።

የእርስዎን ግላዊነት እናከብራለን። በማንኛውም ጊዜ ከደንበኝነት ምዝገባ ይውጡ።