በለጠ ሞላ ጌታሁን(ዶክተር)
የዓብን ሊቀመንበር
"የተሻለች ኢትዮጵያን የሚፈልጉ ኃይሎች እንዲሰባሰቡ ጥረት እናደርጋለን። አገራችን እንድታድግ፣ የዜጎቿ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ ዲሞክራሲዊ ስርዓት እንዲጎለብት የማድረግ ኃላፊነትን ተቀብለን ተነስተናል።"
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች እና ዝመናዎች
የዓብን አዲስ መግለጫ።
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ዓብን የሻቢያ መንግስት በኢትዮጵያ የዉስጥ ጉዳይ የሚያደርገዉ ጣልቃገብነት ቀጥሏል ሲል ገለጸ።
ራዕይ እና ተልዕኳችን
እያንዳንዱ ድምጽ የሚሰማበት፣ እያንዳንዱ ግለሰብ እኩል እድሎች የሚያገኝበት እና ህዝቦች ሁሉን ባሳተፈ አስተዳደር የሚያድጉበትን መንገድ ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል።
- ራዕያችን፣ የፖለቲካ ተሳትፎ ከድምጽ መስጫ ባለፈ ቀጣይነት ያለው የዜጎች ተሳትፎ፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውይይት እና በሁሉም የአስተዳደር እርከኖች ላይ የትብብር ውሳኔዎችን ያካትታል።
- ዴሞክራሲዊ የሆነ ግልጽ አሰራር ለሁሉም ተደራሽ የሚሆንበት፣ የተለያዩ አመለካከቶች ዋጋ የሚሰጡበት፤ ፖሊሲዎች የማህበረሰቡን እውነተኛ ፍላጎቶች እና ምኞቶች የሚያንፀባርቁበትን ምህዳር እንፈጥራለን።
- አመራሩ ግልጽ እና ተጠያቂነት ያለው፣ ማስረጃ እና ስነምግባር የፖሊሲ ልማትን የሚመራበት እና የበለጠ ፍትሃዊ፣ ቀጣይነት ያለው እና የበለጸገ ማህበረሰብን ለአሁኑ እና ለመጪው ትውልድ ትኩረት የሚሰጥበት አሰራር እንዘረጋለን፡፡
- ለአዎንታዊ ማህበራዊ ለውጥ እና እኩልነት ጥምረት መገንባት።
እያደገ ያለው ማህበረሰባችንን ይቀላቀሉ።
ለአዎንታዊ ለውጥ የቆመ እንቅስቃሴ አካል ይሁኑ። ዛሬ ይቀላቀሉን እና ለሁሉም የተሻለ የወደፊት ሁኔታን ለመቅረጽ ያግዙ።
ከአባላቶቻችን አንደበት!
የእኛን ማህበረሰብ የሚወክሉ የተለያዩ ድምፆች
በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን ) ከምስራታው ጀምሮ በተለያዩ ክፍሎች ተመድቤ ሳገለግል የነበረ እና አሁንም በማገልገል ላይ እንደሆኩኝ የሚታወቅ ነው። በዚህም መሰረት ፓርቲያችን አብን በቅደም ተከተል ባስቀመጣቸው ፍኖተ ካርታ በመመራት ህዝብ ከማንቃት ወደ ማደራጀት በመውሰድ የአማራ ህዝብ ጥያቄ በሁሉም ዘንድ እንዲታወቁና ምላሽ እንዲሰጣቸው ታግሎ በማታገልደረጃ ከፍተኛ ድርሻ አለው። በዚህም መሰረት አብን በሰላማዊ ትግልን ውጤት እንደሚገኝ አስተማሪ ድርጅት እንደሆነ የመጣንበት መነሰገድ ያሳያል። ስለሆነም መንግስት የአማራ ህዝብ ጥያቄ በመረዳት አለማቀፍ ተቋሟትም የአማራ ህዝብ ጥያቄን እንዲያውቁ እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጥያቄዎቻችንን ተረድተው የጋራ ሀገራችን ዲሞክራሲያዊ እና የመድበለ ፓርቲ ስርአት የተገነባባት እና አንድነቷ ተጠብቆ ለሁሉም ዜጎቿ ምቹ ሀገር ለመገንባት በትግል ላይ እንገኛለን ።
ኤርሚያስ ተገኝ
ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ አባል
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን) አባል ከሆንኩበት ጊዜ ጀምሮ ዓብን በሀገራችን የሚገባውን ትኩረት ያላገኙ የማህበረሰባችን ክፍል አካልጉዳተኞች ዋና የአካል ጉዳተኞች ህግ ሰራሽ ክፍተቶችን እንዲሴተካከሉ ለመታገል አካል ጉዳተኛን ወደፊት ማምጣት እና በአመራርነት በማካተቱ የህዝብ ድርጅት እንደሆነ የታየበት ሒደት ነው ። አካል ጉዳተኛው በተፈጥሮም ይሁን በሰውሰራሽ በሚታይበት ጉዳት ሲደርስባት የነበረውን የአመለካከት ፣ እነረዲሁም በህግ ማእቀፍ የሚታዩትን መገለል ለማስቆም እንዲሁም በሚፈጠሩ ችግሮች ዋና የግፍ ተቋዳሽ እና ግንባር ቀደም ተጠቂ እንደመሆናቸው በተጨማሪ በአማራነታቸው የሚደርስባቸውን በደል እና መገለል በራሳቸው ድምፅ እንዲያሰሙ እና ውክልናቸው እንዲረጋገጥ የአካታችነትን መርህ ፓርቲያችን አብን በመከተሉ ኩራት ይሰማኛል ። በተለያዩ መድረኮች የአማራ ህዝብ በደል እና በተለይ አካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እና ህግ ወለድ ችግሮች ድምፅ በመሆን እንዲሁም ጥያቄዎቻችን በፖሊሲ ማእቀፍ በሚጋባ የማታገያ አጀንዳ በመሆኑ ወደ ፓርቲው እንድቀላቀል አስገድዶኛል በቀጣይም አካል ጉዳተኞች በማደራጀት በፖለቲካ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ አበክረን እንሰራለን።
አብርሃም አባተ
የአካል ጉዳተኞች ክንፍ አባል
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዓብን) አባል ከሆንኩበት ጊዜ ጀምሮ አብን ሴቶች 50+ የማህበረሰባችን ክፍል እንደመሆናቸው በአሳታፊነት በማካተቱ የህዝብ ድርጅት እንደሆነ የታየበት ነው ። የአማራ ሴት ሲደርስባት የነበረውን ለማስቆም እንዲሁም ዋና የግፍ ተቋዳሽ እና ግንባር ቀደም ተጠቂ እንደመሆኗ ሴቶች የራሳቸውን በደል በራሳቸው ድምፅ እንዲያሰሙ እና ውክልናቸው እንዲረጋገጥ የአካታችነትን መርህ ፓርቲያችን አብን በመከተሉ ኩራት ይሰማኛል ። በተለያዩ መድረኮች የአማራ ህዝብ በደል እና በተለይ ሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ድምፅ መሆን እንዲሁም በሚጋባ የማታገያ አጀንዳ በመሆኑ ትልቅ አክብሮት አለኝ በቀጣይም የሴቶች ተደራሽ ላይ አበክረን እንሰራለን።
ቤተልሄም አበራ
አባል
እንደተዘመኑ ይቆዩ
የቅርብ ጊዜ ዝመናዎችን፣ ዜናዎችን እና የክስተት ማስታወቂያዎችን ለመቀበል ለጋዜጣችን ይመዝገቡ።
የእርስዎን ግላዊነት እናከብራለን። በማንኛውም ጊዜ ከደንበኝነት ምዝገባ ይውጡ።